Wednesday, August 17, 2016

ሥራዬን የሠራህልኝ Serayien Yeserahelegn ዮሴፍ አያሌው Yoseph Ayalew #2

 ዮሴፍ አያሌው Yoseph Ayalew
አዝ፦ ሥራዬን ፡ የሠራህልኝ ፡ መንገዴን ፡ ያቀናህልኝ (፪x)
አማኑኤል ፡ ከፍ ፡ በልልኝ (፫x)
ኢየሱሴ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ

ተራራውን ፡ ንዶ ፡ ሜዳ ፡ ከአደረገው
መራመድ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ ከእኔ ፡ ሚጠበቀው (፪x)

ጐዳናዬ ፡ ቀንቶ ፡ ተራመድ ፡ ብሎኛል
ከእኔ ፡ ጋር ፡ ስላለ ፡ ማን ፡ ይቃወመኛል (፪x)

ማን ፡ ይቃወመኛል (፪x)
የቱ ፡ ይይዘኛል (፪x)

አልፈራም ፡ ልቤ ፡ አይሰጋ
ጌታዬ ፡ አለ ፡ ከእኔ ፡ ጋ
አልፈራም ፡ ልቤ ፡ አይሰጋ
የጠራኝ ፡ አለ ፡ ከእኔ ፡ ጋ
አይቆምም ፡ ምንም ፡ ከፊቴ
እግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ዛሬም ፡ ጉልበቴ (፭x)

አዝ፦ ሥራዬን ፡ የሠራህልኝ ፡ መንገዴን ፡ ያቀናህልኝ (፪x)
አማኑኤል ፡ ከፍ ፡ በልልኝ (፫x)
ኢየሱሴ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ

ሰባሪው ፡ እግዚአብሔር ፡ ከፊት ፡ ወጥቷልና
ሃሳቤ ፡ ተሳክቶ ፡ መንገዴም ፡ ተቃና (፪x)

የነሃሱን ፡ ደጆች ፡ በስልጣን ፡ ሰበረው
እኔም ፡ ሰባብሬ ፡ ከእርሱ ፡ ጋር ፡ አልፌያለው (፪x)

ከእርሱ ፡ ጋር ፡ አልፌያለው (፬x)

አልዝልም ፡ እኔ ፡ አልደክምም
ስራዬ ፡ አያሰለችም (፪x)

ቅባቱ ፡ በእኔ ፡ ስላለ
ይሄዳል ፡ እየጀመረ (፭x)

አዝ፦ ሥራዬን ፡ የሠራህልኝ ፡ መንገዴን ፡ ያቀናህልኝ (፪x)
አማኑኤል ፡ ከፍ ፡ በልልኝ (፫x)
ኢየሱሴ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ

ታማኝ ፡ ነው ፡ የጠራኝ ፡ ጌታ
ለምንም ፡ ትጥቄ ፡ አይፈታ (፪x)

ብርቱ ፡ ነው ፡ በቃሉ ፡ የፀና
ይመራኛል ፡ በድል ፡ ጐዳና (፭x)

አዝ፦ ሥራዬን ፡ የሠራህልኝ ፡ መንገዴን ፡ ያቀናህልኝ (፪x)
አማኑኤል ፡ ከፍ ፡ በልልኝ (፫x)
ኢየሱሴ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ከፍ ፡ በልልኝ

ከፍ ፡ በል ፡ ብል ፡ ሁልጊዜ
ኢሄ ፡ መች ፡ ይበቃሃል (፫x)
ተባረክ ፡ ብል ፡ ሁልጊዜ
ኢሄ ፡ መች ፡ ይበቃሃል (፫x)
ተመለክ ፡ ብል ፡ ሁልጊዜ
ኢሄ ፡ መች ፡ ይበቃሃል (፫x)