Monday, August 8, 2016

የካሳ ዘመን Yekasa Zemen

ቴዎድሮስ  ታደሰ Teodros Tadesse


"ሰማይ ፡ ምድር ፡ ይስማኝ ፡ ፍጥረት ፡ ያድምጠኝ
እግዚአብሔር ፡ ያሰበው ፡ ጸሎቱ ፡ የተሰማ ፡ ያ ፡ ሰው ፡ እኔ ፡ ነኝ
እኔ ፡ ነኝ"

በቆዘምኩበት ፡ ዘመን ፡ ፈንታ
ከፍ ፡ ሊያደርገኝ ፡ ደጉ ፡ ጌታ
መከራዬንም ፡ ሊያስረሳኝ
ቀኑን ፡ ጠብቆ ፡ መጣልኝ

ባለቀስኩበት ፡ ዘመን ፡ ፈንታ
ደግሞ ፡ ሊያስቀኝ ፡ ደጉ ፡ ጌታ
መከራዬንም ፡ ሊያስረሳኝ
ቀኑን ፡ ጠብቆ ፡ መጣልኝ

የካሳ ፡ ዘመን ፡ አለ ፡ ከፊቴ (፪x)
ልውጣ ፡ ልውረሰው ፡ ወግድ ፡ ጠላቴ ፡ ዞርበል ፡ ጠላቴ
የበቀል ፡ ቅባት ፡ ስላረፈብኝ
ኪዳንህ ፡ ፈርሷል ፡ ዳግም ፡ ላትገዛኝ (፪x)

ወራሽ ፡ ሆኜ ፡ ሳለሁ ፡ እርስት ፡ እንደሌለው
የሃዘን ፡ የለቅሶ ፡ ቤቴን ፡ ልታደርገው
ወገን ፡ ዘመን ፡ ያጣ ፡ ባይተዋር ፡ ብቸኛ
ብለህ ፡ ስትጣራ ፡ ጌታ ፡ መጣልኛ
በሰው ፡ አቆጣጠር ፡ ቢመስል ፡ የዘገየ
እውነተኛ ፡ ዳኛ ፡ መገፋቴን ፡ አየ

ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ስማ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁ
በጨለማ ፡ ብሄድ ፡ ጌታ ፡ ብርሃኔ ፡ ነው
የጠራኝ ፡ እግዚአብሔር ፡ አይጥልም ፡ አውቃለሁ

እንዳልሰማ ፡ የአንተን ፡ ስብከት
ውሸታም ፡ ነህ ፡ የውሸት ፡ አባት
ፈጣሪዬን ፡ ለእኔ ፡ ልታማ
ብዙ ፡ ሞከርክ ፡ መች ፡ ልታቅማማ

እኔስ ፡ የማውቀው ፡ ይሄን ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ ለእኔ ፡ መልካም ፡ ነው (እግዚአብሔር ፡ ለእኔ ፡ መልካም) (፬x)

በቆዘምኩበት ፡ ዘመን ፡ ፈንታ
ከፍ ፡ ሊያደርገኝ ፡ ደጉ ፡ ጌታ
መከራዬንም ፡ ሊያስረሳኝ
ቀኑን ፡ ጠብቆ ፡ መጣልኝ

ባለቀስኩበት ፡ ዘመን ፡ ፈንታ
ደግሞ ፡ ሊያስቀኝ ፡ ደጉ ፡ ጌታ
መከራዬንም ፡ ሊያስረሳኝ
ቀኑን ፡ ጠብቆ ፡ መጣልኝ

የካሳ ፡ ዘመን ፡ አለ ፡ ከፊቴ (፪x)
ልውጣ ፡ ልውረሰው ፡ ወግድ ፡ ጠላቴ ፡ ዞርበል ፡ ጠላቴ
የበቀል ፡ ቅባት ፡ ስላረፈብኝ
ኪዳንህ ፡ ፈርሷል ፡ ዳግም ፡ ላትገዛኝ (፪x)

ከላይ ፡ አዞልኛል ፡ የሰማይ ፡ አባቴ
ሞልቶ ፡ እንዲትረፈረፍ ፡ በበረከት ፡ ቤቴ
ከእኔ ፡ ይልቅ ፡ ለእኔ ፡ የሚያስብልኝ
አምላክ ፡ አላኝና ፡ እጅግ ፡ ባለጠጋ
ለምንስ ፡ ልሳቀቅ ፡ እንዴት ፡ ብዬ ፡ ልሥጋ

ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ስማ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁ
በጨለማ ፡ ብሄድ ፡ ጌታ ፡ ብርሃኔ ፡ ነው
የጠራኝ ፡ እግዚአብሔር ፡ አይጥልም ፡ አውቃለሁ

እንዳልሰማ ፡ የአንተን ፡ ስብከት
ውሸታም ፡ ነህ ፡ የውሸት ፡ አባት
ፈጣሪዬን ፡ ለእኔ ፡ ልታማ
ብዙ ፡ ሞከርክ ፡ መች ፡ ልታቅማማ

እኔስ ፡ የማውቀው ፡ ይሄን ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ ለእኔ ፡ መልካም ፡ ነው (እግዚአብሔር ፡ ለእኔ ፡ መልካም) (፬x)